NSLSC Design and Construction Works Office/ ንስላ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ስራዎች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • NSLSC Design and Construction Works Office/ ንስላ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ስራዎች ፅ/ቤት

NSLSC Design and Construction Works Office/  ንስላ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ስራዎች ፅ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from NSLSC Design and Construction Works Office/ ንስላ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ስራዎች ፅ/ቤት, lebu to jemo, Addis Ababa.

Governmental office that build public infrastructure works in Nifas Silk Lafto Sub City under Addis Ababa city Administration and design and construction works bureau

"የአረንጓዴ አሻራ እንክብካቤ  ማድረግ የተተከሉት ችግኞች ለመጪው ትውልድ የአየር ንብረት ለውጥ ሁነኛ ሚና ይጫወታል"የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለመጪው ትውልድ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥርና ተስ...
30/01/2026

"የአረንጓዴ አሻራ እንክብካቤ ማድረግ የተተከሉት ችግኞች ለመጪው ትውልድ የአየር ንብረት ለውጥ ሁነኛ ሚና ይጫወታል"

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለመጪው ትውልድ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥርና ተስፋን የሚሰጥ መሆኑን እና እንክብካቤ መደረግ እንዳለበት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት አስታወቀ።

በዛሬው ዕለት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት አመራርና ሰራተኞች በክረምት አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ ችግኝችን ተንከባክበዋል።

የክፍለ ከተማው ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ አበበ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋን እንዲያድግ፣ የአየር ንብረት ለውጥና የመሬት መንሸራተት አደጋ እንዳይከሰት እያገደረገ ካለው አስተዋፅኦ ባሻገር ውብና ፅዱ እንዲሁም ለዜጎች ምቹ አከባቢን በመፍጠር ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

በመሆኑም ሁሉም አካል የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበት ገልፀዋል።

የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር የነበረው የ46 ሜዳ ግንባታ ተጀመረ ላፍቶ፡ታህሳስ 23/2018፦ በንፋስ ስልክ   ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ የ...
31/12/2025

የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር የነበረው የ46 ሜዳ ግንባታ ተጀመረ

ላፍቶ፡ታህሳስ 23/2018፦ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር የነበረው የ46 ሜዳ ግንባታ ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ካባ መብራቱ፣ የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አቶ መብራቱ ደሴን ጨምሮ የክፍለ ከተማና የወረዳ የስራ ኃላፊዎች ተገኝትዋል ።

በወረዳ 6 ወጣቶች ስብእና መገንቢያ ማዕከል የሚገኘው ሜዳው ከዚህ በፊት በኮንትራክተር ችግር ምክንያት በተሰጠው ጊዜ ማጠናቀቅ ባለመቻሉ ለረጅም አመታት በአካባቢው ወጣቶችና ማህበረሰብ ዘንድ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መቆየቱ ተመላክቷል።

በእለቱ ግንባታውን ከሚያካሂደው ኮንትራክተር ጋር ግንባታውን በ45 ቀናት ውስጥ አጠናቆ እንዲያስረክብ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ካባ መብራቱ ፥ የይሰራልን ጥያቄው የረጅም ጊዜ መሆኑን ገልጸው አሁን ላይ ፕሮጀክቶች እየተጠናቀቁ በሚገኝበት ፍጥነት ልክ ማጠናቀቅ ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም ኮንትራክተሩ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ መሰረት በማጠናቀቅ ባጭር ጊዜ ውስጥ የህብረተስቡ የመልካም አስተዳድር ጥያቄ መልስ ያገኛል ብለዋል።

"መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት ከመቀነስ ባሻገር በመንግስትና ህዝብ መካከል መተማመን እንዲኖር ያደርጋል" ወይዘሮ ካባ መብራቱላፍቶ፣ ህዳር 29/2018:- መሶብ የ...
08/12/2025

"መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት ከመቀነስ ባሻገር በመንግስትና ህዝብ መካከል መተማመን እንዲኖር ያደርጋል" ወይዘሮ ካባ መብራቱ

ላፍቶ፣ ህዳር 29/2018:- መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት ከመቀነስ ባሻገር በመንግስትና ህዝብ መካከል መተማመን እንዲኖር ያደርጋል ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ ገለፁ።

በዛሬው ዕለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጂ+5 ህንፃ ግንባታ ተጀምሯል።

ግንባታው በሁለት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ያላሰለሰ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ የክፍለ ከተማው ዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ግንባታውን ያስጀመሩት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ጥላ ስር ለመስጠትና የተገልጋዮችን እንግልት በመቀነስ ረገድ የሚኖረው ማና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ማዕከሉ የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት፣ ግልፅና ቀልጣፋ ለማድረግና የተገልጋዮችን እርካታ ለመጨመር ከሚኖረው ፋይዳ ባሻገር በመንግስትና በህዝብ መካከል መተማመን እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ክፍለ ከተማው በተለያዩ ወረዳዎች ለሚያከናውነው ግንባታዎች ላለፍት 21ቀናት ሲሸጥ የነበረውን ጨረታ ከፈተ   ላፍቶ፡ህዳር18/2018፦የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግን...
27/11/2025

ክፍለ ከተማው በተለያዩ ወረዳዎች ለሚያከናውነው ግንባታዎች ላለፍት 21ቀናት ሲሸጥ የነበረውን ጨረታ ከፈተ

ላፍቶ፡ህዳር18/2018፦የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት በተለያዩ ወረዳዎች ለሚያከናውነው ግንባታዎች ላለፍት 21ቀናት ሲሸጥ የነበረውን ጨረታ ከፍቷል።

ጨረታ የመክፈት ስነ ስርዓቱ ለ3ተከታታይ ቀናት ተቋራጮችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም በክፍለ ከተማው የሚገኙ የሚመለከታቸው ተቋማትና ተወካዮች እንዲሁም ታዛቢዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

ጨረታው የተካሄደው በ24 ሎት ወይም የስራ አይነት ሲሆን 10ስራዎች በማህበር ዘርፍ እንዲሁም 18የስራ ብዛት ለአማካሪ ተቋራጭና ማህበር ተቋራጮች መሆኑ ተመላክቷል።

የክፍለ ከተማው ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ አዲስ አንበሴ፥ጨረታው ፍትሀዊ እንደነበር ገልጸው የተገኙ ትንንሽ ክፍተቶችን በማሳለፍ አሳታፊ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

አክለውም የጨረታ ሂደቱን ክፍለ ከተማው ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ በመጨረስ በተጠቀሰው ጊዜ ወደ ተግባር እንደሚገባ ገልጸዋል።

መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ መሆኑ በጨረታ ሰነዱ ላይ ተገልጿል።

የክፍለ ከተማው ዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት በኮሪደር ልማት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰራተኞች የእውቅና እና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄደላፍቶ፡ጥቅምት 2/2018 የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከ...
11/11/2025

የክፍለ ከተማው ዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት በኮሪደር ልማት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰራተኞች የእውቅና እና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄደ

ላፍቶ፡ጥቅምት 2/2018 የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት በኮሪደር ልማት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰራተኞች የእውቅና እና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዷል።

እውቅናው በ2ተኛ ዙር ከመካኒሳ ፣ጀርመንና ፤ፉሪ አካባቢ በተሰራው የኮሪደር ልማት ሥራ ላይ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰራተኞች የተሰጠ ነው፡፡

የክፍለ ከተማው ምክር ቤት አፈ -ጉባኤ የሆኑት አቶ ወጋየሁ ኃይሉ በእለቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት ፦በኮሪደር ልማት ስራው ላይ የተሳተፋችሁ ሰራተኞች በሙሉ አሻራችሁን በኃላፊነት ስለተወጣችሁ ልትመሰገኑ ይገባል ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወይነሸት ለማ በበኩላቸው፥ ከአንድ አመት በላይ ባስቆጠረው የኮሪደር ልማት ስራ ላይ ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በልዩ ትኩረት ሌት ተቀን ሲተጋ እንደነበር አስታውሰው ለነበረው የጋራ ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አክለውም እውቅናና ሽልማቱ በቢሮም ከቢሮ ውጭ ሆነው ሲሰሩ ለነበሩ ሰራተኞች እውቅና ከመስጠት ባለፈ ለቀጣይ ተልዕኮ የሚያዘጋጅ ነው ብለዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው አፈ -ጉባኤ የሆኑት አቶ ወጋየሁ ኃይሉ የክፍለ ዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወይነሸት ለማ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ከሳር ቤት ጀርመን፣ ጋርመንት፣ፉሪ አካባቢ የኮሪደር ልማት በቅርቡ ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃቱ የሚታወስ ነው።

ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመንት ፉሪ  የሚዘልቀው የኮሪደር ልማት ምን ምን አካቷል?*******************•  እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ  16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ (በተ...
25/10/2025

ከሳርቤት - ጀርመን አደባባይ- ጋርመንት ፉሪ የሚዘልቀው የኮሪደር ልማት ምን ምን አካቷል?
*******************

• እስከ 60 ሜትር የሚሰፋ 16.5 ኪ.ሜ አስፓልት መንገድ (በተጨማሪ 3 .5 ኪ. ሜ የውስጥ ለውስጥ መንገድ) አለው፣

• 33 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ

• 13.3 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ

• 21 የተለያዩ ፕላዛዎች

• ክረምት ከበጋ ፣ በቀን እና በምሽት አገልግሎት የሚሰጡ 20 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች

• 20 የልጆች መጫወቻ ቦታዎች

• 5.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት

• 20 የመኪና ማቆሚያ ቦታና ተርሚናሎች ፣ 1 የመኪና ቻርጂንግ ስቴሽን

• በግለሰቦች እና በመንግስት የተገነቡ 1,107 የንግድ ቤቶች

• 50.5 ሄክታር ስፋት ያላቸዉ አረንጓዴ ቦታዎች

• 40 የሕዝብ መፀዳጃ ቤቶች

• 38 የታክሲና አውቶቡስ ቤይ

• 13 ካፌዎች እና 1 ሬስቶራንት እንዲሁም ከ 1 ሄክታር በላይ የነርሰሪ ቦታን በዉስጡ አካትቶ ይዟል።

እንኳን ደስ አላችሁ/ እንኳን ደስ አለን!ክፍለ ከተማው በ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት የአረንጓዴ ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነላፍቶ ሐምሌ 14/2017:- የንፋስ ስልክ ...
21/07/2025

እንኳን ደስ አላችሁ/ እንኳን ደስ አለን!

ክፍለ ከተማው በ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት የአረንጓዴ ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ

ላፍቶ ሐምሌ 14/2017:- የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በ2017 በጀት አመት አፈጻጸም ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 5ኛ ደረጃን በመያዝ የአረንጓዴ ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።

በመድረኩም የህዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች እውቅናና ሽልማት ተበርክቷል።

በዚሁም መሰረት፦

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፦
1ኛ. ወረዳ ቱሉ ኤጀርሳ
2ኛ. ወረዳ ጀሞ
3ኛ ወረዳ 12 ዘመናዊ ተሽከርካሪ ተሸላሚ ሆነዋል።

እውቅናና ሽልማቱ ላይ በተላለፈው መልእክት ይህ እውቅና የሁሉም አመራር፣ በየደረጃው ያሉ ባለሞያዎች እና የባለድርሻ አካላት የተሰጠ ሲሆን ይህም ይበልጥ በመስራት የህዝቡን የመልማት ፍላጎት የምናሳካበት መሆኑ በሽልማት መድረኩ ላይ በክብርት ከንቲባ አዳነች አበቤ ተገልጿል።

ክብርት ከንቲባዋ አክለውም ይህ የተሰጠው እውቅና በቀጣይ በጀት ዓመት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርትተን እንድንሰራ የተሰጠ አደራም ጭምር ነው ብለዋል።

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ በበኩላቸው ክፍለ ከተማው ከነበረበት ክፍተት አንፃር በብዙ መሻሻሉንና በርካታ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል

ክፍለ ከተማው ላስመዘገበው የላቀ አፈጻጽም በክፍለ ከተማው በየደረጃው ላሉ አመራሮች ፣ ባለሙያዎች እና ነዋሪዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Communication

21/07/2025
2017 በጀት  የትምህርት ፕሮጀክት
18/07/2025

2017 በጀት የትምህርት ፕሮጀክት

በመትከል ማንሰራራት
18/07/2025

በመትከል ማንሰራራት

Address

Lebu To Jemo
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NSLSC Design and Construction Works Office/ ንስላ ዲዛይንና ኮንስትራክሽን ስራዎች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share