14/08/2026
ኢንተርፕራይዙ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አዳዲስ ገልባጭ መኪኖችን አስገባ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነሃሴ 09 ቀን 2018 ዓ.ም
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ቅልጥፍናና ዕድገት ማሽነሪዎች ያላቸው ሚና ከፍተኛ ነው። ይህንን ብሔራዊ ዓላማ በመከተል መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለሥራ አገልግሎት የሚውሉ የ2024/ 2025 አዲስ ሞዴል 20 ዘመናዊ ገልባጭ መኪኖችን ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ገዝቶ ወደ ሥራ አስገብቷል።
የኢንተርፕራይዙ የግንባታ መሳሪያዎችና ተሽከርካሪዎች አስተዳደር እና ጥገና መምሪያ ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ሀብታሙ ደሬሳ እንደገለጹት፦
በአሁኑ ወቅት የአንድ ገልባጭ መኪና ወርሃዊ ኪራይ እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ መሆኑን ጠቁመው አዲሶቹ መኪኖች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ በዓመት ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን ያስችላሉ።
ተሽከርካሪዎቹ በጂፒኤስ (GPS) የታገዘ የደህንነት ቁጥጥርና ክትትል የሚደረግላቸው በመሆኑ የብልሽት ቅነሳ እንዲኖር ያስችላሉ።
ግዥው የኢንተርፕራይዙን የመፈጸም አቅም ከማሳደጉም በላይ፣ ለሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ጊዜንና ገንዘብን በመቆጠብ የደንበኞችን እርካታ እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል።
በመጨረሻም ተሽከርካሪዎቹ የሀገር ሀብት ጭምር በመሆናቸው፣ ምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታቸውን ሳይጨርሱ ለብልሽት እንዳይዳረጉ ሠራተኞችና የሥራ አመራሮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ዘጋቢ ማርታ ተፈሪ
ፎቶግራፍ መሳይ ያደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
https://dfmc.mod.gov.et/
https://youtube.com/-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
https://www.facebook.com/fdredefense.official