17/06/2026
ይርጋለም ኮንስትራክሽን በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በይርጋዓለም የተ/የግብ/ኢን/ ፓርክ ተጨማሪ ሦስት አዳዲስ ፕሮጀክቶች ትግበራ ላይ የውል ስምምነት ተፈራረመ።
የኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል ዱባለ ድርጅቶች ውስጥ የሆኑት የሦስት ፕሮጀክቶች ትግበራ ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈርሟል፡፡
ቀደም ሲል በ”Golden organic Avocado oil’’ ምርት ላይ ተሰማርተው ያሉት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል በዛሬው ዕለት ስምምነቱን የፈረሙት በፓርኩ ተጨማሪ ሶስት ፕሮጀክቶች ማለትም በዘርፈብዙ የጥራጥሬ ዘይት፣ የድፍድፍ ዘይት ማጣሪያ እና የተቀናጀ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በ12.8 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወይንም 2 ቢሊዮን ብር የሚፈጁ ፕሮጀክቶች ሲሆኑ፤ በሙሉ አቅም ወደ ሲራ ሲገባ ለ500 ያህል ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ይሆናል፡፡
የውል ስምምነቱን የፈረሙት ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ኃይሉ የተራ እንደገለጹት በፓርኩ የሀገር ውስጥ ባለሀብት በዚህ ያህል ካፒታል ፕሮጀክት ሲፈረም የመጀመሪያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ እጅግ ትልቅ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች መሆናቸውንም አመላክተዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆኑት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ ቀደም ሲል በነበረው የአቮካዶ ዘይት ፕሮጀክት ተበረታተው የጀመሯቸው መሆኑን ገልፀው፤ የሶስቱንም ፕሮጀክቶች ሼድ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቀው ወደ ምርት ሂደት እንደሚገቡ አረጋግጠዋል፡፡
የድርጅታችን ሰራተኞችና ማናኔጅምነት አካላት እንኳን ደስ አለን፣ አላችሁ!
የረዳን ፈጣሪ ይመስገን!
በጋራ ኢትዮጵያን እንገነባለን!
ይርጋለም ኮንስትራክሽን