Ethiopian Construction Design and Supervision Works Corporation

Ethiopian Construction Design and Supervision Works Corporation Consultancy firm The leading and the largest consulting firm in the water sector consultancy business in the country

20/08/2019

324 ሚሊዮን አተረፈ
======
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2011 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት ብር 325 ሚሊዮን ለማትረፍ አቅዶ ብር 324 ሚሊዮን ወይም ከዕቅዱ 100.5 በመቶ አተረፈ፡፡ ይህ ትርፍ ከ2010 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ15 በመቶ ብልጫ አለው፡፡
ኮርፖሬሽኑ ይህንን ትርፍ ሊያገኝ የቻለው በዕቅድ ዘመኑ በውሃና ኢነርጂ፣በህንጻና ከተማ ልማት፣በትራንስፖርት፣በጂኦቴክኒካል ምህንድስና፣ በቅየሳና ጂኦስፓሻል፣በምርምር፣ላብራቶሪ እና ስልጠና ዘርፎች ሊያከናውን ከያዛቸው የዲዛይን፣የቁጥጥርና የማማከር ተግባራት ብር 1.09 ቢሊዮን ገቢ ለማግኘት አቅዶ ብር 769.1 ሚሊዮን ወይም የዕቅዱን 70 በመቶ ገቢ በማግኘቱ እንደሆነ የኮርፖሬሽኑ ዕቅድ አፈጻጸም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ነሐሴ 14 ቀን 2011 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ በተገመገመበት ወቅት ተገልጿል፡፡

19/02/2019

የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱቨርቪዥን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የግማሽ በጀት ዓመት አፈጻጸም ተገመገመ
===============
ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ተጠሪ ከሆኑት የልማት ኮርፖሬሽኖችና ድርጅቶች መካከል አንዱ የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኮረረፖሬሽን ሲሆን፣ የ2011 በጀት ዓመት የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙ የካቲት 11 ቀን 2011 ዓ.ም. በኤጀንሲው መሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ተገምግሟል፡፡

ለግማሽ ቀን የተካሄደውን የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ በየነ ገ/መስቀል መርተውታል፡፡ ለግምገማ መነሻ የሚሆን ሪፖርት ያቀረቡት የኮርፓሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ነገደ አባተ ናቸው፡፡

ኮርፖሬሽኑ በውሃና ኢነርጂ፤ በሕንጻና ከተማ፣ በትራንስፖርት፣ በጂኦቴክኒክ፣ በላብራቶሪና ምርመራ እና በቅየሳ ጂኦስፖሻልና ሲቪል ኢንፎርማቲክ ዘርፎች ተዋቅሮ የዲዛይንና ሱፐርቪዥንና የላብራቶሪ ምርመራ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ በ2011 ግማሽ በጀት ዓመት ከእነዚህ አገልግሎቶች በድምሩ ብር 546 ሚሊዮን ገቢ ለማግኘት አቅዶ አፈጻጸሙ ብር 338.42 ሆኗል፡፡ ይህ አፈጻጸም ከዓመቱ ዕቅድ 62 በመቶ ሲሆን፤ ከስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ደግሞ 76 በመቶ መሆኑ በግምገማው ወቅት ተወስቷል፡፡

በትርፍ ረገድ ኮርፖሬሽኑ በግማሽ ዓመት ከታክስ በፊት ብር 164.56 ሚሊዮን ለማትረፍ አቅዶ ብር 141.79 ወይም የዕቅዱን 86 በመቶ ገቢራዊ አድርጋል፡፡ ለገቢውም ሆነ ለትርፉ ትልቁን ድርሻ የያዘው የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ መሆኑ በግምገማው ወቅት ተገልጿል፡፡
በግምገማው ማጠቃለያ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ በየነ ገ/መስቀል ኮርፖርሽኑ የዕቅዱን አፈጻጸም በሚዛናዊ ውጤት ተኮር (BSC) መሠረት መመዘኑ፤ የየዘርፎችን የዕቅድ አፈጻጸም ድርሻ መለየቱ እና ሠራተኛውም ለተገኘው ገቢና ትርፍ በአማካይ ያለው ድርሻ ምን ያህል እንደሆነ ማመላከቱ ጠንካራ ጎኖቹ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ የኮርፖሬሽኑ አፈጻጸም ከዕቅዱ አንጻር ዝቅ ያለ ቢሆንም፤ በአፈጻጸም ወቅት ተከስተው ከነበሩ ልዩ ልዩ ሁኔታዎች አንጻር ሲታይ ውጤቱ ጥሩ እንደሆነ ገልጸው ኮርፖሬሽኑ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የሚያስችል የማካካሻ ዕቅድ ይዞ መንቀሳቀስ እንዳለበት አቅጣጫ ሰጥተው ግምገማው ተጠናቋል፡፡

31/08/2018

ማት ድርጅቶች ሚኒስትር ከሁለት ኮርፖሬሽኖች የሥራ አመራር አባላት ጋር ተወያዩ
===============================================
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ክቡር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን እና ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር አባላት ጋር ያካሄዱት ውይይት በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ በሚኒስቴሩ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲሆን፣ ውይይቱም የተኮረው በ2011 በጀት ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም ላይ ነው፡፡ በዚህ ውይይት ክቡር አቶ ጌታቸው ባልቻ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚኒስቴር ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪና ግብርና ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ፣ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሚኒሰቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ አመራሮች፣ የኮርፖሩሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንዳወቅ አብቴ እና ሌሎች የሥራ አመራር አባላት ተገኝተዋል፡፡
የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ታሳቢዎችንና መነሻዎችን እንዲሁም የትኩረት አቅጣጫዎችን ክቡር አምባሰደር ተሸመ ቶጋ በዝርዝር ገልጸው፣ ኮርፖሬሽኑ እነዚህን መሠረት አድርጎ በዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ ማከናወን የሚገባውን ተግባራት አስከ ነሐሴ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ማጠናቀቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ የኮርፖሬሽኑ የሥራ መሪዎችም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸማቸው ያለበትን ደረጃ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ክቡር ሚኒስትሩ በ2011 በጀት ዓመት በለውጥ ሥራዎች ረገድ ኮርፖሬሽኑ ትኩረት ሰጥቶ ማከናወን ያለበት በስኳር ኢንዱስትሪው ዙሪያ ያሉ ችግሮችን ከመሠረቱ መፍታት ሊሆን እንደሚገባ፣ በመካሄድ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችም እንዲጠናቀቁ ዕቅዱን በየደረጃው እስከ ሠራተኛው ድረስ አውርዶ በጥብቅ የአፈጻጸም ክትትልና ዲሲፒሊን በሙሉ አቅሙ እንዲንቀሳቀስ አመራር ሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
ከሰዓት በኋላ ባለው ክፍለ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ከክብርት ወ/ሮ ምሥራቅ ማሞ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚኒስቴር የማዕድን፣ኢነርጅና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እና ከሌሎች የሚኒስቴሩ ሥራ አመራሮች ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን ላብራቶሪን ተዟዙረው ጎብኝተዋል፡፡ ከጉብንታቸውም በኋላ በኮርፖሬሽኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተገኝተው ስለኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ ገለጻ በዋና ሥራ አስፈጻሚው በዶ/ር ነገደ አባተ ገለጻ ተድረጎላቸው ከኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር አባላት ጋር በኮርፖሬሽኑ የ2010 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2011 ዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ ዙርያ ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱም ማጠቃለያ ኮርፖሬሽኑ ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ለማከናወን እያደረገ ያለው ጥረት፣የተማረ የሰው ኃይል መያዝ መቻሉ፣አመራሩ ከሠራተኛው ጋር መግባባትን ፈጥሮ የተቀናጀ ሥራ እየሠራ መሆኑ እና በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ እንደ ታንዛንያና ናይጄሪያ ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ገብቶ መሥራቱ የሚደነቅና የሚበረታታ መሆኑን ክቡር ሚኒስትሩ ጠቅሰው፣ ሌሎችም የልማት ተቋማት ከዚህ መማር እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ሴቶችን ወደ አመራር ደረጃ በማምጣት ረገድ ኮርፖሬሽኑ የሚቀረው በመሆኑ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ በመጨረሻም የ2011 ዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት በአግባቡ መፈጸማቸውን ኮርፖሬሽኑ እንዲያረጋግጥ አመራር ሰጥተው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

29/09/2017

Happy New Year!

29/09/2017
28/06/2016

Tendaho Dam and Irrigation Project
On-Works /Quaternary Canal Construction/

27/06/2016

የርብ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት

Koga Dam and Irrigation Project 3D Model Simulated video
26/05/2016

Koga Dam and Irrigation Project 3D Model Simulated video

educational

Address

24 Street
Addis Ababa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Construction Design and Supervision Works Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Construction Design and Supervision Works Corporation:

Share