EEU Deder Customer Service Center

EEU Deder Customer Service Center Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from EEU Deder Customer Service Center, Deder.

27/02/2026
29/10/2023
Ethiopian Electric Utility Deder Customer Service Center covers two districts and twenty-seven rural towns and is servin...
28/10/2023

Ethiopian Electric Utility Deder Customer Service Center covers two districts and twenty-seven rural towns and is serving the community day and night with its few employees.

24/08/2022

ለፍጆታ የተሰጠን የኤሌክትሪክ ኃይል ያላግባብ መጠቀም ጉዳቱና ተጠያቂነት
************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ጥራት ያለው ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ የክፍያ ስርዓት ተግባራዊ ከማድረጉ ጎን ለጎን ተከታታይነት ያላቸው የሱፐርቪዥንና የቆጣሪ ምርመራ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

መሰል ስራ መሰራቱ የኃይል ብክነቶችን ለመቀነሰ እንዲሁም ለፍጆታ የተሰጠን የኤሌክትሪክ ኃይል ያላግባብ በሚጠቀሙ ደንበኞች ላይ ተገቢ የሆኑ ማስተካከያዎችን ለማድረግም ያስችላል፡፡

ያላግባብ የሆነ አጠቃቀም ደግሞ ለደንበኞች የሚቀረበውን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቋረጥና እንዲዋዥቅ የሚያደርግ ሲሆን፤ በደንበኛውም ሆነ በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል፡፡

በተጨማሪም ደንበኛውን ለቅጣት፣ ለወጪና ለተጠያቂነት እንዲሁም ተቋሙንም ለኪሳራ የሚዳርግ ተግባር ነው፡፡

ይህ ድርጊት ከሚያስከትለው ጉዳት ጎን ለጎን በተጠቃሚው ላይ የፍትሐ ብሔር እና የወንጀል ተጠያቂነትም ያስከትላል፡፡

በመሆኑም ማንኛው ደንበኛ ለፍጆታ የተሰጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል በአግባቡ መጠቀምና ያላግባብ የሆነ አጠቃቀምንም ከመከላከል አንፃር የራሱን ሚና መወጣት ይኖርበታል፡፡

ከዚህም አንዱ በቅድሚያ ከተቋሙ ጋር ውል ፈፅሞ ኤሌክትሪክ እንዲጠቀም ቆጣሪ የተፈቀደለት ማንኛውም ደንበኛ ተገቢ የሆነ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ መሰል ድርጊት ሊከላከል ይገባል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ያለው ቤት ግዥ የሚፈፅም ግለሰብ ቤቱን ከመረከቡ በፊት በአቅራቢያ በሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመቅረብ ውዝፍ የፍጆታ ዕዳዎችን ማጣራት፣ ቆጣሪው ከወንጀል ድርጊት የፀዳ መሆኑን ማረጋገጥ እና ከተቋሙ ጋር ውል እንደገና ማደስ ይጠበቅበታል፡፡

ህግን ከማስከበር አኳያ እንዲሁም በደንበኞች የሚፈፀሙ ያላግባቡ የኃይል አጠቃቀም ለመከላከል እና ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ እንደ ሃገር የኢነርጂ አዋጅ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ ውሏል፡፡

በኢነርጂ አዋጁ አዋጅ ቁጥር 810/2006 መሰረት ማንኛውም ግለሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል የሰረቀ፣ በሕገ ወጥ መንገድ ከሌላ ጋር ያገናኘ፣ መስመር ያሰናከለ ወይም የኤሌክትሪክ ኃይል ኢንዲሰረቅ ከሌላ መስመር ጋር እንዲገናኝ ወይም መስመሩ እንዲሰናከል ያደረገ ወይም መስመሩ የተሰረቀ፣ በሕገወጥ መንገድ ከሌላ መስመር ጋር የተገናኘ ወይም የተሰናከለ መሆኑ እያወቀ ከዚሁ መስመር ማናቸውም የኤሌክትሪክ ኃይል ለፍጆታ ያዋለ ወይም የተገለገለ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ከተፈቀደለት የኃይል አጠቃቀም ውጭ ሲጠቀም የተገኘ ማንኛውም ደንበኛ በሃገሪቱ የኢነርጂ አዋጅ መሰረት በህግ ተጠያቂ እንደሚሆን ይህ አዋጁ በግልፅ ይደነግጋል፡፡

አዋጁን ተላልፎ ያላግባብ የኤሌክትሪክ ኃይል ሲጠቀም የተገኘ ማንኛውም አካል በሕግ ከመጠየቁም በተጨማሪ ይጠቀምበት የነበረው ቆጣሪ እንደሚቋረጥበት እና ያላግባብ ለተጠቀመው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በታሪፉ መሰረት ተሰልቶ ከዳግም ማስቀጠያ ክፍያ እና ከቅጣት ገንዘብ ጋር እንዲከፈል ይደረጋል፡፡

ስለሆነም ከመሰል ቅጣትና ተጠያቂነት ለመዳን እንዲሁም የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከል ማንኛውም ደንበኛ የሚገለገልበትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ከተቋሙ ጋር በገባው ውል መሰረት ብቻ እንዲጠቀምና ቤት አካራዮችም በየጊዜው አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር እንዲያደርጉ ተቋሙ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም ከቆጣሪ ጋር የተገናኘ ማንኛውም አይነት ችግር ካጋጠመ በአካባቢ ወደ ሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመቅረብ ወይም በ905 ነፃ የጥሪ ስልክ በመደወል ጥቆማ መስጠት ይቻላል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Address

Deder

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EEU Deder Customer Service Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share